ምስጋና

ምስጋና
ምስጋና በክርስትና ህይወት ውስጥ ትልቅ ቦታ ያለው ነው:: በቤተ ክርስቲያን ጸሎቶቻችን በአብዛኛው በምስጋና ጀምረው በምስጋና ይጨርሳሉ::
ጸሎት ከምስጋና ጋር ነው የሚቀርበው:
ፊል 4:6 ጌታ ቅርብ ነው። በነገር ሁሉ በጸሎትና በምልጃ ከምስጋና ጋር በእግዚአብሔር ዘንድ ልመናችሁን አስታውቁ እንጂ በአንዳች አትጨነቁ።
ባስሊዎስ ቅዳሴ :ለእኛ በጎ ነገርን ያደረገ እግዚአብሄርን እናመሰግነዋለን:: ይቅርባይ የጌታችን የአማላካችንና የመድሃኒታችን አባት ሰውሮናልና ረድቶናልና ጠብቆ አቅርቦናልና:: ወደ እርሱም ተቀብሎናልና አጽንቶ ጠብቆናልና:: እስከዚህ ሰዓት አድርሶናልና:: ስለ ስራው ሁሉ በስራው ሁሉ

በቤተ ክርስቲያን ጸሎቶች በአጠቃላይ በለቅሶ ቤት/ፍትሃት ሳይቀር በምስጋና ይጀመራሉ በምስጋናም ያልቃሉ::
መዝ 7፡17 እግዚአብሔርን እንደ ጽድቁ መጠን አመሰግናለሁ፥ ለልዑል እግዚአብሔርም ስም እዘምራለሁ።

ምስጋና ለአምላክ የሚቀርብ መስዋእት ነው::
መዝ 116: 17 (ሙሉው) ለአንተ የምስጋና መሥዋዕትን እሠዋለሁ፥ የእግዚአብሔርንም ስም እጠራለሁ። መዝ 107: 22 የምስጋና መሥዋዕትንም ይሠውለት፥ በእልልታም ሥራውን ይንገሩ።
እግዚአብሔርን ልናመሰግነው ከሚገባን ምክነያቶች መካክል: ስለፈጠረን ፡ ስለ ድንቅ ችሎታው ፡ በተፈጥሮችን ስለሰጠን ችሎታዎች፡ በህይወት ስለመኖራችን ፡ ክርስቲያን ስለመሆናችን ፡ እንደ ሃጢያታችን ስላልተመለከተን፡ ጤና ስለሰጠን፡ በህመም ስላስተማረን)

የምስጋና ደረጃዎች : በአመስጋኞችን አይነት በሶስት ከፍለን እናየዋለን (በጥቂቱ ነገር የሚያመሰግኑ፡ ከመከራ ሲወጡ/ ደግ ነገር ሲደረግላቸው የሚያመሰግኑና በመከራ ውስጥም ቢሆን የሚያመሰግኑ)

በመጀመሪያ በማናቸውም ሁኔታ ቢሆን የማያመሰግኑ ሰዎች አሉ:: እግዚአብሄር ታምራት ቢያደርግላቸው ከፈተና ቢያወጣቸውም ምስጋና ትዝ የማይላቸው ሰዎች አሉ::
ዘጠኙ ለምጻሞች የዚህ ምሳሌ ናቸው::
ሉቃ 17፡15_18 ጌታ ካነጻቸው 10 ለምጻሞች ውስጥ ለምስጋና የተመለሰው አንዱ ብቻ ነው:: ከእነርሱም አንዱ እንደ ተፈወሰ ባየ ጊዜ በታላቅ ድምፅ እግዚአብሔርን እያከበረ ተመለሰ፥እያመሰገነውም በእግሩ ፊት በግንባሩ ወደቀ፤ እርሱም ሳምራዊ ነበረ።ኢየሱስም መልሶ፦ አሥሩ አልነጹምን? ዘጠኙስ ወዴት አሉ?

ምስጋና የማናመሰግን ሰዎች ችግራችን
• በእኛ አይን ብቻ ስለምናየው ነው (በእነ ማርታ አይን አላዛር ሞቷል በክርስቶስ በኩል ግን ለክብር ነበር)
• የተደረገልንን ነገር ስለማናስተውልም ጭምር ነው (ስለጤናችን ስራ ስለመያዛችን ትዳር ስለመመስረታችን በክርስትና ህይወት ስለመኖራችን ምን ያክል እናመሰግናለን?) እንደ እኛ የሆኑ ብዙዎች ነበሩ ግን እኛ ያለንበት መድረስ ያቃታቸው::

በጥቂቱ የእግዚአብሔር ስራ ምስጋና ከአፋቸው የማይቋረጥ : ከጉንፋን ስለዳኑ ተኝተው ስለተነሱ እግዚአብሔርን የሚባርኩ አሉ:: እኛ ከማናውቀው እርሱ ከሚያውቀው መከራና ፈተና ስለሰወረን::
ስለመፈጠራቸው የሚያመሰግኑ መዝ 139:14 ግሩምና ድንቅ ሆኜ ተፈጥሬአለሁና አመሰግንሃለሁ ሥራህ ድንቅ ነው፥ ነፍሴም እጅግ ታውቀዋለች። ባለው የሚያመሰግን የሚደሰት ልብ ያስፈልገናል::

ከችግር ከመከራ ከበሽታ ሲድኑ /ስጦታ ሲቀበሉ ምስጋና የሚያቀርቡ:
ከችግር እግዚአብሄር ሲያወጣቸው ከፈተና ሲሰውራቸው ወይንም ልዩ ነገር እግዚአብሔር ሲያደርግላቸው የሚያመሰግኑ አሉ:: አንዱ ለምጻም እንዳደረገው:: ብዙ ክርስቲያኖች ይህንን ያደርጋሉ::
በመከራ ውስጥ እያሉ የሚያመሰግኑ: በዚህ የምስጋና ህይወት የሚታዩ በተለይ ወደ እግዚአብሔር የበለጠ የቀረቡ ቅዱሳን ሰዎች ናቸው:: የስድብና የማንጎራጎር ሳይሆን የምስጋና ቃል ብቻ ከአፋቸው የሚወጣ::
ያእ 5፡11 እነሆ፥ በትዕግሥት የጸኑትን ብፁዓን እንላቸዋለን፤ ኢዮብ እንደ ታገሠ ሰምታችኋል፥ ጌታም እንደ ፈጸመለት አይታችኋል፤ ጌታ እጅግ የሚምር የሚራራም ነውና።

በመከራ ሆነው እያመሰገኑ የኖሩትን እናመሰግናቸዋለን በጹአን እንላቸዋለን::

መዝ 33:1 ጻድቃን ሆይ፥ በእግዚአብሔር ደስ ይበላችሁ ለቅኖች ምስጋና ይገባል።

ምስጋና ለአንድ ቀን ወይም በአንድ ሁኔታ ብቻ የሚቀርብ ሳይሆን በሁሉ ስለሁሉ የሚደረግ ነው
ምስጋና ስለሁሉ በሁሉ
1ኛ ተሰ 5:17 ሳታቋርጡ ጸልዩ፤ በሁሉ አመስግኑ፤ ይህ የእግዚአብሔር ፈቃድ በክርስቶስ ኢየሱስ ወደ እናንተ ነውና።
ቆላ 3:17 እግዚአብሔር አብን በእርሱ እያመሰገናችሁ፥ በቃል ቢሆን ወይም በሥራ የምታደርጉትን ሁሉ በጌታ በኢየሱስ ስም አድርጉት።
ስለሁሉ የምናመሰግነው ነገር ሁሉ ለበጎ እንደሆነ ስለምናምን ነው: ሮሜ 8:28 ሆኖም አንዳንዴ ነገሮች ለበጎ መሆናቸውን ለማመን እንቸገራለን
የዮሴፍ መሽጥ ለበጎ ነበረ ነገር ግን ያእቆብም ይሁን ዮሴፍ አልቅሰዋል ዘፍ 37:28
ከእግዚአብሄር የሚሰጠን ሁሉ ለበጎ ነው በክፉዎች ሰዎች ብንወድቅ እንኳን እግዚአብሔር ወደ በጎ ነገር ሊለውጠው ይችላል::
የጎደለን ብቻ ሳይሆን የሆነልንንም እንመልከት:: ወደ ዓለም ምንም አላመጣንም ምንም አንወስድም እግዚአብሔር ግን ብዙ ነገር ስጥቶናል::

እግዚአብሔርን የምናመሰግንበት መንገድ:
በጸሎት: በመዝሙራችን ፡በንግግራችን፡በሰላምታችን ፡ በአጠቃላይ በልባችን እናመስግን::
ለአለን ነገር ጥሩ ግንዛቤ ይኑረን
የጎደለንን እያሰብን ለማሟላት እንስራ ባለን ነገር ደግሞ እግዚአብሔርን እናመስግን

Advertisement

Leave a Reply

Fill in your details below or click an icon to log in:

WordPress.com Logo

You are commenting using your WordPress.com account. Log Out / Change )

Twitter picture

You are commenting using your Twitter account. Log Out / Change )

Facebook photo

You are commenting using your Facebook account. Log Out / Change )

Connecting to %s


Follow

Get every new post delivered to your Inbox.