ሰሞኑን የዜና ማሰራጫዎች የካቶሊክ ቀሳውስት ያደረጉትን የህጻናት መድፈር በማረጋገጥ ቤተ ክርስቲያኗ በአደባባይ ይቅርታ እንድትጠይቅ አድርገዋል። ይህ በትክክል ለማነኛቸውም አካል ውርደት ነው። ለቤተ ክርስቲያኗ ፤ ለቀሳውስቱ ፤ ለተደፋሪዎች ህጻናት ፤ለቤተሰቦቻቸውና በካቶሊክ ውስጥ ድርሻ ያላቸው ሰዎች ሁሉ ያፈሩበት ነው። ሆኖም ዘገባዎች እንዳመለከቱት ይህ አይነት ድርጊት አሁን ቢባባስም የቆየ እንደነበረ አንዳንዶች ይናገራሉ። ታዲያ ሳይቃጠል በቅጠል እንዲሉ ቅድመ ክትትል ባለማደረጓና በጊዜው እርምት ባለመውሰዷ ከ500 የሚበልጡ የህጻናትን መድፈር የክስ ኬዞች ተመዝግበው ይገኛሉ። http://news.bbc.co.uk/2/hi/europe/8577740.stm
በእኛ ቤተ ክርስቲያንም ምንም አንኳን አብዛኛዎቹ አባቶቻችን ጨዋዎችና እግዚአብሔርን በፍጹም ልባቸው ከማገልገል ውጭ ሌላ የማያውቁ ቢሆንም አንዳንዶች በተለይም ደግሞ ራሳቸውን ባህታውያን ብለው ከሚጠሩት ወገኖች የሚያታልሉ እንዳሉ አንዳንድ ሰዎች ይናገራሉ። እኔ በአይኔ ባላየውም አንድ ባህታዊ የዛሬ አንድ አመት አካባቢ አስገድዶ በመድፈርና በግድያ ክስ ተከሶ እንደተያዘ ሰምቻለሁ። ታዲያ ምዕመናኑ እንዲህ አይነት ሰዎችን በተለይም ቄስ ሳይሆኑ ቄስ ነኝ ባህታዊ ሳይሆኑ ባህታዊ ነኝ የሚሉና በክርስቶስ መንፈስ ሳይሆን በስጋ መንፈስ የሚመሩ ሰዎችን ሊያውቅባቸውና ሊያጋልጣቸው ይገባል። ሐሰተኞችን ካላጋለጥንና ቻሌንጅ ካላደረግን ከጊዜ በሗላ እውነተኞችንም እንደ ሐሰተኞች ቆጥረን እንድንጠላ ያደርገናል። ማነኛውንም አይነት አቢዩዝ ሰምቶ ዝም ከማለት ማጣራቱና ለሚመለከተው ክፍል ማሳወቁ ለቤተ ክርስቲያኗም ይሁን ለሰውየው ጠቀሜታው የጎላ ነው ብየ አምናለሁ።
Please forward your ideas on the issue.
March 22, 2010 at 4:45 am |
Yes there are some people like the mentioned bahtawi who try to foolish our sisters. Our sisters have to be aware of such things.
March 27, 2010 at 7:23 pm |
“ከካቶሊክ ቤተ ክርስቲያን sex abuse ምን እንማራለን?”
I didnot supported this issue in my idea. B/se the idea based on our church kahinate has no any evedence in you context. So, this is not good mentioned for our church.